tg-me.com/nibab_lehiwot/157
Last Update:
የእኔ ታሪክ (ምዕራፍ -2 )
ክፍል 6
ቪቪያን ከ እናቷ ጋ እየተነጋገረች ነው። እማዬ እንዴት ልንገረው......... በጣም ጭንቅ እንዳላት ከፊቷ ያስታውቃል። ልጄ በጭራሽ ይሄንን ነገር ከአባትሽ እንድትደብቂ አልፈልግም ዛሬ ትንሽ መስሎ የተደበቀው ነገር ነው ለነገ ሌላ ትልቅ መዘዝ ይዞብን የሚመጣው። ችግርን ሳያድግ ነው ከስሩ መቁረጥ....... ግን አቋሙኮ ያስፈራል ቢከለክለኝስ? ምንም ይሁን ንገሪው ቪቫን እናቷ ተቆጣች። እሽ እማየ አሁን እነግረዋለሁ አለች አይኖቿን እያቁለጨለጨች( ቪቪያን ፀጉሯ በጣም ለስላሳ እና ረጅም ክብ ፊት እና ትልልቅ አይኖች ያሏት ውብ ሴት ነች)። ሕዝቅኤል እንደሚለው ፀጉሯ የራቢያን ፀጉር ያስታውሰዋል።
ከእናቷ ጋ ተለያይታ በረንዳ ወደተቀመጠው አባቷ በቀስታ ተራመደች።
አባዬ አንድ የምነግርህ ነገር ነበረ..... እና ንገሪኛ የኔ ትንሽ ርግብ በስስት ያያታል። ቪቪያን ለእሱ ልጁ ብቻ አይደለችም ሳቋ ሳያስደስታቸው የሞቱት እናቱ ንግግሯ አባቱን ፣ እልከኝነቷ ሳይጠግበው የተለየው ጓደኛውን፣አይኗ ያቺ ትንሽ የነበረችው እህቱን፣ ፀጉሯ ሳያገኝ ያጣው ፍቅሩን(ልጁን) ብቻ በቪቪያን ውስጥ ሕዝቅኤል ሙሉ ህይወቱን ያያል።እሷ ሁሉ ነገሩ ናት። ለሕዝቅኤል መኖር የ ቪቪያን መኖር ግዴታ ነው።
ግን አትቆጣኝማ አለች ፈገግ ብላ ጉንጩን እየሳመች። አንቺ አጭበርባሪ ምን አድርገሽ ነው አላት እድሜም ብቻ ሳይሆን ሀዘን ያጨማደደው ከንፈሩን በግድ ፈገግ እያደረገ። እሷም ሁልጊዜ እንደምታደርገው እግሩ ስር ተቀምጣ ራሷን ጭኑ ላይ አስደገፈች ህዝቅኤልም በተመሳሳይ ሁሌ እንደሚያደርገው ለስላሳ ፀጉሯን መዳሰስ ጀመረ። አባ አሁን አድጌያለሁ እና ፍቅረኛ ይዣለሁ በቃ እኔ ካንተ ምንም ልደብቅ አልችልም። ሕዝቅኤል ያልጠበቀው ነገር ስለነበር ደነገጠ እውነትም ልጄ አድጋለች። አለ በውስጡ ምነው አባ አትመልስልኝም እንዴ?..... እሱ ሲደነግጥ እሷም ተርበተበተች። ሕዝቅኤል ግን ያስደነገጠው ፍቅረኛ መያዟ አልነበረም ከዛ በኋላ ቤቱን ጥላ መውጣቷ እንጅ.......ቤት ውስጥ ከሌለች ምን እንደሚሆን ሲያስብ ጨነቀው።
ርግብ ሁሌ ከእኔ ጋ አትኖሪምኮ አንችም የራስሽን ሕይወት መኖር አለብሽ። ቪቪያን ደስ አላት። ባይሆን የልጄን ልብ ያሸነፈው ማን ነው?
ሁለተኛው ከባድ ጥያቄ ሆነ ለቪቪያን ። ምክኒያቱም ሕዝቅኤል በጭራሽ እንደማይቀበላት ታውቃለች። ግን የግድ መናገር ስለነበረባት እንደምንም ተርበትብታ ተናገረች። አ...አያን......
ምን...........ሕዝቅኤል ጮኸ።
ይቀጥላል ...........
@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot
BY ሕይወትን - በገፅ
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/nibab_lehiwot/157